የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የአመራር አባላት ኢንተርፕርነርሽፕ ክህሎት መጎልበት ለፈጠራና ለለውጥ መሠረት ነው- ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦የአመራር አባላቱ ኢንተርፕርነርሽፕ ክህሎት መጎልበት ለፈጠራና ለለውጥ መሠረት ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት "አመራርና የመጪው ዘመን ዝግጁነት "በሚል መሪ ሀሳብ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።


ሥልጠናው የአመራር አባላት ሥራቸውን በአንተርፕረነርሽፕ አስተሳሰብ እንዲመሩና ለተለዋዋጭ የሥራ አካባቢዎች ዝግጁ እንዲሆኑ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ ተመላክቷል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ በዚሁ ወቅት ሥልጠናው የምክር ቤት አባላት ካላችሁ የላቀ የሕዝብ አመራር ልምድ በመነሳት ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በላቀ ብስለትና በሥራ ፈጠራነት መንፈስ እንድትቀርጹ ለማገዝ ነው ብለዋል።

አባላቱ ያላቸው ዕውቀትና ልምድ ውጤታማ እና ፍሬያማ የሆኑ ሥራዎች ለመስራት የሚያግዝ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ይህም ችግሮችን በፈጠራ፣ በፍጥነት እንዲሁም በባለቤትነት መንፈስ ለመፍታትና አዳዲስ የአገልግሎት ዘርፎችን ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።


የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በበኩላቸው፤ የዘመኑን ፈጣን ለውጥ ለመቋቋም የአመራሩ የሥራ መርህ መዘመን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

የአመራር አባላት እንደ አንድ ሥራ ፈጣሪ የችግሮችን መፍትሔ በአዲስ የፈጠራ መንገድ የመቅረጽ፣አዳዲስ ዕድሎችን የመለየት እና በሥራ ሂደት ውስጥ የመፍጠንና የመፍጠር ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባም ገልጸዋል።

በመሆኑም ይህ ሥልጠና በምክር ቤቱ አባላት ዘንድ የስትራቴጂክ አመራር ክህሎትን ከማሳደጉ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ግቦችን በብቃት ለማሳካት የሚረዳ የተቀናጀ የአሠራር ሥርዓት ለመገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የምክር ቤቱ አባላትና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025