
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ እና ግብዓት አጠቃቀምን በማሻሻል እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን በማላመድ የዘርፉን ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
የምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትናና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው፤ የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚያሻ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በተለይ በመኸር እርሻ የተመዘገበውን አመርቂ ውጤት በበልግ አዝመራ ሥራ በመድገም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የተጀመረውን ሽግግር ማፅናት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ለዚህ ደግሞ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲሰራ ማሳሰባቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
ለታለመው የበልግ አዝመራ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራ እና ሌሎችም ኢንሼቲቮች አመራሩና ባለሙያው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲሰሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025