
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ እና ግብዓት አጠቃቀምን በማሻሻል እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን በማላመድ የዘርፉን ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
የምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትናና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው፤ የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚያሻ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በተለይ በመኸር እርሻ የተመዘገበውን አመርቂ ውጤት በበልግ አዝመራ ሥራ በመድገም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የተጀመረውን ሽግግር ማፅናት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ለዚህ ደግሞ አመራሩ በቁርጠኝነት እንዲሰራ ማሳሰባቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
ለታለመው የበልግ አዝመራ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሻራ እና ሌሎችም ኢንሼቲቮች አመራሩና ባለሙያው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲሰሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026