🔇Unmute
ሀላባ ቁሊቶ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በወተትና በዶሮ ልማት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመርሐ-ግብሩ ተሳታፊዎች ገለጹ።

ወጣት አብድልቃድር ሲራጅ እንደገለጸው፤ ከጓደኞቹ ጋር ተደራጅተው በተሠማሩበት የዶሮ ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ ሆነዋል።
በዚህም መሠረት አሁን ከ1 ሺህ በላይ ዶሮዎች እንዳላቸው እና በቀን እስከ 900 እንቁላል ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን አረጋግጧል።

ካፒታላቸው 3 ሚሊየን ብር ማለፉን እና ከ15 ለሚልቁ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም ገልጿል።
ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ አየለች ካሳ በበኩላቸው፤ በተሠማሩበት የከብት ዕርባታ ዘርፍ ውጤታማ በመሆን አሁን ላይ 10 የወተት ላሞችና 13 ጥጃዎች እንዳሏቸው ገልጸዋል።

በቀን ከ90 ሊትር በላይ ወተት ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያቸውን እያሳደጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር በእንስስት ሀብት ዘርፍ ያለውን ዐቅም ወደ ውጤት እንዲቀየር በማስቻል ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሀላባ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ሀጂ ኑሪዬ ናቸው።

የዘርፉን ስኬታማነት ለማሳደግ ዝርያ የማሻሻል፣ የእንስሳት ጤና አጠባበቅና አመጋገብ ላይ እየተሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ከ17 በላይ የወተት፣ ከ21 በላይ የዶሮ እና ከ10 በላይ የማር መንደሮች መኖራቸውንም አብራርተዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026