🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የሀገሪቷን ኢኮኖሚ ዕድገት በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስቀጠል ወሳኝ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የምጣኔ ሀብት ምሁራን ገለጹ።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ ነው
የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የባህር በር አልባ መሆኗ ለወጪና ገቢ ንግድ የምታወጣውን ወጪ እጅግ ከፍተኛ እንዲሆን አድርጎታል።
በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ጀማል መሀመድ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በፈጠራና በፍጥነት ላይ የተመሰረተ አስደማሚ የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ ዓይነቱ ግዙፍ ዓመታዊ ዕድገት በዓለምም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚታይ መሆኑን የጠቀሱት ተመራማሪው፣ ሀገሪቱ ያላትን ከፍተኛ ምርታማነትና የልማት ስኬት አብራርተዋል።
ይሁን እንጂ ሀገሪቱ አሁን ያላትን እምቅ አቅም እና የህዝብ ቁጥር ያገናዘበ ዕድገት እንዲኖራት ለበርካታ አስርት ዓመታት ያጣችውን የባህር በር ባለቤትነት ማረጋገጥ የግድ እንደሚላት አመልክተዋል።
ለዚህም እንደ ቬትናም ያሉ ሀገራትን ተሞክሮ በማንሳት፣ የወደብ ተደራሽነት ለወጪ ንግድ ዕድገትና ለኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ያለውን ወሳኝ ፋይዳ በአብነት ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ ወደብ ቢኖራት አሁን የሚታየውን ኢኮኖሚያዊ እድገት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳድገው የጠቆሙት ተመራማሪው፤ በዚህም የወደብ ጉዳይ ለሀገራዊ ጥቅምና ለዜጎች ኑሮ መሻሻል መሰረታዊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የባህር በር ባለቤትነት መረጋገጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ለመጣው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር ዘላቂና አስተማማኝ የሆነ የኢኮኖሚ መፍትሄ እንደሚያመጣ አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር ከፍተኛ ተመራማሪ ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣የባሕር በር አለመኖር የኢትዮጵያን የወጪ ንግድ እንቅስቃሴ በሌሎች ሀገራት ፍላጎት ላይ ጥገኛ እንዲሆን በማድረግ በኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑ አስረድተዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ ተፈጥሯዊ መብቷ የሆነውን የባሕር በር ባለቤትነት ካረጋገጠች የንግድ እንቅስቃሴዋን በማሳለጥ የትራንስፖርት ወጪን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የባሕር በር ባለቤት መሆን የንግድ ተወዳዳሪነትን ከመጨመሩም በላይ የኢኮኖሚውን እድገት ቀጣይነት ለማረጋገጥ መሠረታዊ መፍትሔ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025