የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመኸር እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ተደራሽ እየተደረገ ነው

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመኸር እርሻ የሚሆን የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ግብርና ቢሮ የግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር ተስፋዬ በቀለ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በክልሉ ለዘንድሮው የመኸር እርሻ የሚውል 131 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል።

እስከአሁን ድረስም 98 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በአሶሳ ከተማ እና መተከል ዞን በሚገኙ ማከማቻ መጋዘኖች እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የአፈር ማዳበሪያው በወቅቱ መድረሱ አርሶ አደሩ የመኸር እርሻ ዝግጅቱን ከመጀመሩ በፊት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲያከናውን ጊዜ የሚሰጥ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

የአፈር ማዳበሪያ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ የአርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎት እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።

ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በየወረዳው በተደለደለው ኮታ መሠረት አርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያውን እንደሚወስድ ተናግረዋል።

ከአርሶ አደሩ በተጨማሪ በትልልቅ የእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሃብቶች የአፈር ማዳበሪያ እንዲያገኙ በማድረግ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።

ከአፈር ማዳበሪያ በተጨማሪ የምርጥ ዘር ግብዓት በቅርቡ ወደ ክልሉ እንደሚገባም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025