የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ ተወስዷል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ ፤ የካቲት 30 /2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑ ተገለጸ።

በክልሉ ኮንትሮባንድ እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን በመከላከል ጤናማ የገበያ ሥርአት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቷል

የክልሉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በነገው እለት የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት ፎረም አስመልክተው ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ለማቅረብ በመቻሉ በርካታ ባለሃብቶችን ለመሳብ እየተቻለ መሆኑን አብራርተዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 226 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰደው ወደ ሥራ ገብተዋል ነው ያሉት።

ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ እየተካሔደ ያለው የድጋፍና የክትትል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ኮሚሽነሯ የገለጹት።

በአሁኑ ወቅትም ለኢንቨስትመንት መሬት ተረክበው ወደልማት ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በተለዩ 81 ፕሮጀክቶች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን 13 ሺህ 600 ሄክታር መሬት ወደ መሬት ባንክ ለማስገባት መቻሉን አስታውቀዋል።

በነገው እለት የሚካሔደው የኢንቨስትመንት ፎረም ከባለሀብቶች ጋር ውይይቶችን በማድረግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል።

በመሆኑም ባለሀብቶች በክልሉ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ በመጠቀም በኢንዱስትሪ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ላይ በመሰማራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025