የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የዓድዋ ድል የትናንት ታሪካችን ብቻ ሳይሆን የነገ እድገትና አንድነታችን መሰረት ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ የካቲት 23/2018(ኢዜአ)፦የዓድዋ ድል የትናንት ታሪካችን ብቻ ሳይሆን የነገ እድገትና አንድነታችን መሰረት ነው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ያሳዩትን አኩሪ ገድል የዘመኑ ትውልድ በልማቱ ሊደግመው ይገባል

130ኛው የዓድዋ ድል በዓል "ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ" በሚል መሪ ሀሳብ በዲላ ከተማ ተከብሯል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ የዓድዋ ድል የሀገር ማንሰራራት የሚጸናበት የነጻነት ቀን ነው።

ዓድዋ ያለፈ የድል ታሪካችን ብቻ ሳይሆን የነገ እድገትና አንድነት መሰረት መሆኑን አንስተው፣ በአሁኑ ወቅትም ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የልማት ጉዞን ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።

ህብረ ብሔራዊነትን ለአብሮነትና ለሀገራዊ እድገት በመጠቀም በተለያዩ የልማት ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

በተለይ በክልሉ የሚገኙ ጸጋዎችን አቀናጀቶ በመጠቀም ከራስ ባለፈ ትርፍ አምራች የመሆን ጥረትን ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


ዓድዋ ጀግኖች አርበኞች የሕይወት መስዋዕትነት ጭምር ከፍለው የጥቁር ህዝብን ትርክት የቀየሩበት ደማቅ የጀግንነት ታሪክ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የዲላ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ታሪኩ በየነ ናቸው።

ድሉ የነጻነትና የአንድነት ምልክት መሆኑን አንስተው እኛም ከዓድዋ ጀግኖች በመማር የድህነት ታሪካችንን መቀየር አለብን ብለዋል።

በዲላ ከተማ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በማጠናከር እድገትን ለማፋጠን በትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል።

የዓድዋ ድል በፓናል ውይይትና በተለያዩ ኪናዊ ዝግጅቶች የተከበረ ሲሆን ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የመከላከያ ሠራዊት አባላት ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025