የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወራቤ ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።

በስልጤ ዞን የተገነባው የሚቶ ኤድነባ መስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።



በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማእረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ሃላፊ መሃመድ ኑርዬ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በክልሉ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።


የውሃ አማራጮችን በመጠቀም የመስኖ ልማት በመተግበር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማጎልበት መቻሉን ጠቁመዋል።

ዛሬ ወደ ስራ የገባው የሚቶ ኤድነባ መስኖ ፕሮጀክት የዚሁ አካል መሆኑን አንስተዋል።

ከፍተኛ ወጪ ወጥቶባቸው የተገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲቆይ ህብረተሰቡ በተገቢው መንገድ መጠቀም እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ካሳዬ ተክሌ፤በተያዘው በጀት አመት በክልሉ 12 የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል።


የሚቶ ኤደነባ የመስኖ ፕሮጀክትም በተያዘለት 6 ወራት ጊዜ ውስጥ ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ 54 ሄክታር ማሳ እንደሚያለማና 200 አባወራ እና እማወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

የከርሰ ምድር ውሀን በፀሃይ ሃይል በመሳብ ለመስኖ አገልግሎት እንዲውል የሚያደርገው ፕሮጀክቱ ከ105 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገበትም ገልጸዋል።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፤ አርሶ አደሮች ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በዘመናዊ መንገድ አልምተው የቤት ውስጥ ፍጆታን በማሟላት ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች ላይ በማተኮር ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።


የመስኖ ፕሮጀክቱን ከሚጠቀሙ አርሶ አደሮች መካከል አቶ አብድልሰላም ሃሰን ከሁለት ሄክታር በላይ መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ ማልማታቸውን ተናግረዋል።

ሌላው አርሶ አደር ሃጅ ዋበላ ተማም በአራት ሄክታር መሬታቸው ላይ ሰብል እና አትክልት ማምረት መጀመራቸውን ገልጸው የመስኖ ፕሮጀክቱን በአግባቡ በመያዝ አገልግሎት እንዲሰጥ በተገቢው መንገድ እንደሚጠቀሙ ተናግረዋል።


በእለቱም የወራቤ ከተማ አስተዳደር ውስጥ እየተከናወነ ያለው የ1 ነጥብ 6 ኪ.ሜ እንዲሁም ከሚቶ -ባራ- ቡልቡላ ድረስ እየተገነባ ያለው የ38 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ ያለበት ሁኔታ እንዲሁም የወራቤ ከተማ የወንዝ ዳርቻ ልማት ጉብኝት ተደርጓል።

በስነስርዓቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስልጤ ዞን የስራ ሃላፊዎች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025