የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሕገወጥ ንግድ ላይ በተሰማሩ ከ133 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ጥር 14 /2018(ኢዜአ)፦በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት በሕገ-ወጥ ንግድ ላይ በተሰማሩ ከ133 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

የሚኒስቴሩ የ2018 ግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የሴክተር ጉባኤ በደሴ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፣ ተቋማቸው ባለፉት ስድስት ወራት ገበያ በማረጋጋት፣ ህገ ወጥ ንግድን በመቆጣጠርና የወጪ ንግድን ለማሳደግ በትኩረት ሲሰራ ቆይቷል።

ገበያን ለማረጋጋት የገበያ ማዕከላትን ለማስፋትና ደረጃቸውን ለማሻሻል የተደረጉ ጥረቶችም ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን ተናግረዋል።

በዚህም የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ግሽበትን ወደ ነጠላ አሃዝ ዝቅ ማድረግ መቻሉ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ነው የገለጹት።

በበጀት ዓመቱ ሰድስት ወራት በሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ በተሰማሩ ከ133 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን ለአብነት በማንሳት።

በሀገሪቱ ጤናማ የንግድ ሥርዓት በመፍጠር ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የወጪ ንግዱን ለማሳለጥ በተደረገ ጥረትም ባለፉት ስድስት ወራት ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቅሰዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በክልሉ ህገ ወጥ ንግድን ለመቆጣጠርና ገበያን ለማረጋጋት በተሰራው ስራ ውጤት መመዝገቡን አንስተዋል።

ሁለገብ ዘመናዊ የገበያ መሰረት ልማት በመገንባት ውጤታማ የንግድ ሥርዓት ለመፍጠር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ባዩሽ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ በክልሉ ገበያን በማረጋጋትና ጤናማ የንግድ ውድድር መፍጠር የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ መደረጋቸውን ገልጸዋል።

በመድረኩ የፌዴራል፣ የክልልና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025