የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሳልጡ የሪፎርም ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ ታህሳስ 1/2018(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ዘመኑን የሚመጥን ለማድረግ የሚያስችሉ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ገለጸ።

በቢሮው የሪፎርም ድጋፍና ክትትል ዳይሬክተር አቶ እንዳላማው ይታይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ከሃምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የታገዘና ወቅቱን የሚመጥን እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ ነው።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የፀደቀውን የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ መሰረት በማድረግ ከፌደራል መንግስቱ ተናባቢ በሆነ አግባብ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ግልጽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ የህዝብን አገልግሎት የማግኘት ፍላጎት በሚያረካና ቅሬታዎችን ሊመልስ በሚችል መልኩ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።


የአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ፣ ግልጽ፣ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ፣ ዲጂታላይዝድና ዘመኑን የሚመጥን መሆን እንደሚጠበቅበት ገልጸው፤ ይህንን ታሳቢ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

ሪፎርሙ ብዝሃነትና አካታችነት ያለው፣ ነጻና ገለልተኛ እንዲሆን ጭምር ተደርጎ እየተሰራ ያለው።

ሪፎርሙ ለተመደበበት ሙያ ብቁና ዲጂታላይዝድ የሆነ ሲቪል ሰርቫንት መፍጠርን መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ቅቡልነት ያለው የመንግስት ሰራተኛ እንዲኖር ያስችላል ብለዋል።

ብቃት ያለው አመራር፣ ባለሙያና ተቋም በመፍጠር ተዓማኒነት ያለው አገልግሎትን መዘርጋት ግድ የሚልበት ጊዜ መሆኑን ገልጸው "መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

ከሪፎርም ስራዎች መካከል አንዱ "መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም በክልል ደረጃ እንዲሁም በባህር ዳርና ደሴ ከተማ አስተዳደሮች ተመርቆ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል።


የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ግልጽና በርካታ ጉዳዮችን በአንድ ጊዜ እልባት የሚሰጥና ህብረተሰቡ ባለበት ቦታ ሆኖ ያለምንም እንግልት አገልግሎቱን እንዲያገኝ ያስቻለ የሪፎርሙ አካል ነው ብለዋል።

በሌሎች አካባቢዎችም እስከ ወረዳ ድረስ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ማጣራት፣ የባለሙያውን የአቅም ክፍተት በተለያዩ ስልጠናዎች ማብቃትና ተዓማኒና ግልጽ የሆነ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት የሪፎርሙ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።

የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርሙ ሦስት ዓመት የሚወስድ መሆኑን ጠቅሰው፤ በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025