የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የጥናትና ምርምር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግና ችግሮችን ለመፍታት አቅም መሆን አለባቸው</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ ፤ጥር 23/2017 (ኢዜአ):- በምሁራን የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግና ችግሮችን ለመፍታት አቅም ከመሆን ባለፈ መንግስት ለሚነድፋቸው ፖሊሲዎች ግብዓት መሆን እንዳለባቸው ተገለፀ።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ብሔራዊ ጥቅሞቻችንና ቀጣናዊ ትስስር ለሚዛናዊ የህዝቦች ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።


በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጅሀድ ናስር እንደገለፁት፤ በዩኒቨርሲቲ ምሁራን የሚያደርጉት የጥናትና ምርምር ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማሳደግና ችግሮችን ለመፍታት አቅም ከመሆን ባለፈ መንግስት ለሚነድፋቸው ፖሊሲዎች ግብዓት ሊሆኑ ይገባል።


በውይይት መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴርን በመወከል የተገኙት በተቋሙ የብሔራዊ መግባባት ባለሙያ ወይዘሮ ሲሳይ ብርሌ እንዳሉት ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት የምሁራን ሚና የላቀ ነው።

የዛሬው ውይይትም ለሀገር እድገት ግብዓት የሚሆኑ የጥናት ውጤቶችንና አማራጭ ሀሳቦችን ምሁራን የሚያፈልቁበት አጋጣሚን የማመቻቸት ዓላማ እንዳለውና መሰል መድረኮችም በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚካሄዱ ተናግረዋል።


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ችሮታው አየለ (ዶ/ር) እንዳሉት ምሁራን ሀገርና ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የምርምር ስራዎችን መስራት ይጠበቅባቸዋል።

መድረኩ ምሁራን ለቀጣናዊ ትስስሮችና ለሀገር ግንባታ ያላቸውን አበርክቶ ለማጉላት የዳበረ ምክረ ሀሳብ ማቅረብ እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል።

በዩኒቨርሲቲው የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ተመራማሪ ዳኜ ሽብሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት በኢትዮጵያ ሰላምን፣ ልማትንና ብልጽግናን ለማምጣት ከቀጣናው ሀገራት ጋር ተባብሮና ተደጋግፎ መስራት ያስፈልጋል።


የኢትዮጵያ ሰላም ለቀጣናው ሰላምና ልማት መጠናከር የላቀ ሚና ስላለው ለተግባራዊነቱም ቀጣናዊ ትብብር ላይ መስራት የግድ እንደሚል ተናግረዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴርና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተወካዮችና የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025