የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በክልሎች ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፉን ለማዘመን ቴክኖሎጂ መር አሰራሮች ተዘርግተዋል</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ጥር 21/2017 (ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት አገልግሎትን ዘርፉን ለማዘመን በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮች መዘርጋታቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የክልልና የከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮዎች ገለጹ።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የኦሮሚያ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ሀላፊዎች የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመን በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር እየዘረጉ ነው።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑርዬ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማሳለጥና ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል።

በህዝብ መናኽሪያዎች ተገልጋዩን የሚያንገላቱና ከታሪፍ በላይ ክፍያን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል።

በ11 መናኸሪያዎች የኤሌክትሮኒክ ትኬት(ኢ-ትኬት) አገልግሎት መተግበሩን ገልጸው፤ ይህን በሌሎች መናኸሪያዎች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የመንጃ ፍቃድና የአሽከርካሪዎች ስልጠና አገልግሎቱን ከኪራይ ሰብሳቢነት የጸዳ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች እንደላ ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ቸርነት በበኩላቸው አገልግሎቱን ለማዘመን በክፍያ፣ በተሽከርካሪ ስምሪት፣ በመንጃ ፍቃድ እድሳት፣ በተሽከርካሪ የቴክኒክ ፍተሻና የቦሎ አሰጣጥ የአንድ መስኮት አገልግሎት መጀመሩን አመልክተዋል።

የመንጃ ፍቃድን ህጋዊነት ለመቆጣጠርም የ'ኦን ላይን' ምዝገባ ቋት መዘጋጀቱን ገልጸው፤ የአሸከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማትንና የቦሎ አገልግሎትን በሲሲቲቪ ካሜራ በመከታተል የሥነ ምግባር ችግሮች ቁጥጥር እየተደረገ ስለመሆኑ አስረድተዋል።

በክልሉ በ290 መናኸሪያዎች ላይ የኢ-ትኬት አገልግሎት በማስጀመር ህብረተሰቡን ከእንግልትና አላስፈላጊ ወጪ መታደግ ተችሏ ብለዋል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ወርቁ ደስታ፤ በመዲናዋ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ለማሳለጥ በተለይ የከተማ አውቶቢስ ሪፎርም ማድረጉን ጠቅሰዋል።

የትራንስፖርት ምልልሱን በመጨመር ህብረተሰቡ በፍጥነት አገልግሎት ማግኘት የሚችልበት አሰራር መዘርጋቱን አስታውቀዋል።

የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት ብቃትን ለማሳደግም በቴክኖሎጂ የታገዘ ጠንካራ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የስድስት ወር የዕቅድ አፈፈፃፀም ግምገማ ተጠሪ ተቋማት፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮዎች እና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት መድረክ በቅርቡ በአዳማ መካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025