
ቡታጅራ፤ ጥር 21/2017 ዓ/ም (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት 30 ሺህ 955 ዜጎች በኮደርስ ስልጠና መሳተፋቸውን የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀምና በቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫ ላይ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት 30 ሺህ 955 ዜጎች በኮደርስ ስልጠና ተሳትፈዋል፡፡
ከዚህ ውስጥ ከ15 ሺህ በላይ የሚሆኑት ስርተፊኬት መውሰዳቸውን ገልጸው ቀሪዎቹ ደግሞ በስልጠና ሂደት ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
በመንግሥት ተቋማት የሚገኙ ሰልጣኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ሌሎች ወጣቶችም ከተለያዩ ኩባንያዎች ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ በበጀት ዓመቱ 49 ሺህ 571 የሚሆኑ ዜጎች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የቢሮው ከፍተኛ አመራር አባላት፤ የዞንና የልዩ ወረዳ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ናቸው፡፡
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025