የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በክልሉ በስድስት ወራት ውስጥ ከ30 ሺህ በላይ ዜጎች የኮደርስ ስልጠና ወስደዋል</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ፤ ጥር 21/2017 ዓ/ም (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት 30 ሺህ 955 ዜጎች በኮደርስ ስልጠና መሳተፋቸውን የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ፡፡

ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀምና በቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫ ላይ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡

የቢሮው ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት 30 ሺህ 955 ዜጎች በኮደርስ ስልጠና ተሳትፈዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ ከ15 ሺህ በላይ የሚሆኑት ስርተፊኬት መውሰዳቸውን ገልጸው ቀሪዎቹ ደግሞ በስልጠና ሂደት ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

በመንግሥት ተቋማት የሚገኙ ሰልጣኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ሌሎች ወጣቶችም ከተለያዩ ኩባንያዎች ጋር ተቀናጅተው እንዲሰሩ መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡

በክልሉ በበጀት ዓመቱ 49 ሺህ 571 የሚሆኑ ዜጎች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ የቢሮው ከፍተኛ አመራር አባላት፤ የዞንና የልዩ ወረዳ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026