የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የኮትዲቭዋር የመንግስት ልዑክ በአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አሰራርና አደረጃጀት ላይ ከኢትዮጵያ የልምድ ልውውጥ አደረገ</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ የኮትዲቭዋር የመንግስት ልዑካን በአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አሰራርና አደረጃጀት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የልምድ ልውውጥ አድርጓል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ የኮትዲቭዋር መንግስት ልዑካን ቡድንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ልዑኩ በቀጣይ ቀናት የአግሮ እንዱስትሪ ፓርኮችን እንደሚጎበኝም ተገልጿል።

የልዑኩ ጉብኝት አላማ በኢትዮጵያ ያሉ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን አሰራርና አደረጃጀት አስመልክቶ ተሞክሮ ለመቅሰም እንደሆነ ተገልጿል።

አቶ ሀሰን የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አደረጃጀትና አሰራር፣ የወጪ ንግድ ድርሻ፣ የስራ እድል ፈጠራ አበርክቶ እና ተጓዳኝ ጉዳዮችን አስመልክቶ ለልዑኩ ገለጻ አድርገዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያና ኮትዲቭዋር በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚያደርጉት የልምድ ልውውጥ ለሁለቱም ሀገራት የቴክኖሎጂ ሽግግርና ቀጣይነት ላለው ዕድገት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ገልጸዋል።

የኮትዲቭዋር መንግስት ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን አደረጃጀትና አሰራር ማድነቁን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025