
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ የኮትዲቭዋር የመንግስት ልዑካን በአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አሰራርና አደረጃጀት ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የልምድ ልውውጥ አድርጓል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ የኮትዲቭዋር መንግስት ልዑካን ቡድንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ልዑኩ በቀጣይ ቀናት የአግሮ እንዱስትሪ ፓርኮችን እንደሚጎበኝም ተገልጿል።
የልዑኩ ጉብኝት አላማ በኢትዮጵያ ያሉ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን አሰራርና አደረጃጀት አስመልክቶ ተሞክሮ ለመቅሰም እንደሆነ ተገልጿል።
አቶ ሀሰን የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አደረጃጀትና አሰራር፣ የወጪ ንግድ ድርሻ፣ የስራ እድል ፈጠራ አበርክቶ እና ተጓዳኝ ጉዳዮችን አስመልክቶ ለልዑኩ ገለጻ አድርገዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያና ኮትዲቭዋር በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚያደርጉት የልምድ ልውውጥ ለሁለቱም ሀገራት የቴክኖሎጂ ሽግግርና ቀጣይነት ላለው ዕድገት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ገልጸዋል።
የኮትዲቭዋር መንግስት ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን አደረጃጀትና አሰራር ማድነቁን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025