
አዲስ አበባ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እና ሕገ-ወጥነትን ወደ ሕጋዊ አሰራሮች የመለሰ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሸን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ኢትዮጵያን ከብድር ጫና የሚያላቅቅ መሆኑን ሚኒስትሩ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ መግባቷ ዘላቂ የልማት ፋይናንስ በመፍጠር ለበርካታ ዘርፎች መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል።
በሀገሪቱ የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚን መፍጠር፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ሴክተሩን ማሻሻል እንዲሁም የዘርፎችን ምርታማነት በማሳደግ የመንግስትን የማስፈፀም አቅም መጨመር የማሻሻያው የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሆኑ አብራርተዋል።
የውጭ ምንዛሬ ዋጋ በገበያው እንዲተመን መደረጉ፣ አምራቾች የልፋታቸውን እንዲያገኙ እንዲሁም ኮንትሮባንድና መሰል ሕገ-ወጥ ተግባራት እንዲገቱ የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል።
በዚህም የወጪ ንግድ እድገትን በታለመለት መልኩ ማስኬድ መቻሉን አንስተዋል።
ማሻሻያው የባንኮች የቁጠባ መጠን እንዲጨምር ማድረጉንም ጠቁመው፥ ብሔራዊ ባንክ ከቀደመው ጊዜ በበለጠ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እንዲኖረው ማስቻሉን ነው ሚኒስትሩ የገለጹት።
ማሻሻያው ምቹ የኢኮኖሚ መደላድል የፈጠረ እና ሕገ ወጥነትን ወደ ሕጋዊ አሰራሮች የመለሰ ነው ብለዋል።
የወርቅ አምራቾች በዓለም አቀፍ የዋጋ ተመን በመሸጣቸው ወርቅን በኮንትሮባንድ ከመሸጥ ይልቅ ለማዕከላዊ ገበያ ለብሔራዊ ባንክ እንዲሸጡ መነሳሳት መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡
በዚህም ብሔራዊ ባንክ በታሪኩ ከፍተኛ የወርቅ መጠን በመግዛት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
መንግስት ለአፈር ማዳበሪያ፣ ለነዳጅ፣ ለዘይት፣ ለመሰረታዊ ሸቀጦች፣ ለመንግስት ሰራተኞች ደሞወዝ እና ለከተማ እና ገጠር ሴፍቲኔት የሚውል በዓመት ከ400 ቢሊዮን ብር በላይ መንግስት ድጎማ ማድረጉን ተናግረዋል።
በቀጣይም ምርታማነትን ማሳድግ እና ማሻሻያውን በታለመለት መልኩ ማስኬድ የትኩረት አቅጣጫዎች ሆነው እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025