የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ክልሉ በስድስት ወራት ውስጥ ከ2 ሺህ 747 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ አደረገ</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ጥር 8 /2017 (ኢዜአ)፡-ጋምቤላ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ2 ሺህ 747 ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ገለፀ።

ክንውኑ ከዕቅዱ በአራት ዕጥፍ ብልጫ እንዳለው ተመልክቷል።

የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጁሉ ጊሎ እንደገለጹት፤ ከለውጡ ወዲህ የክልሉን ሰፊ የወርቅ ማዕድን ከብክነት በመታደግ ጥቅም ላይ ለማዋል ሰፊ ጥረት እየተደረገ ነው።

በሀገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያው የብዝሃ ኢኮኖሚ ትኩረቶች መካከል ማዕድን አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዘርፉ በተሰጠው ትኩረትም እንደ ክልል ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን አስረድተዋል።

ባለፉት ስድስት ወራት በባህላዊ እና በወርቅ አምራች ኩባንያዎች ከ2 ሺህ 747 ኪሎግራም በላይ የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ተልኳል ብለዋል።

አፈጻጸሙ ከዕቅዱ አራት ዕጥፍ በላይ እንደሆነ ተናግረዋል።

በቴክኖሎጂ የታገዘ የወርቅ ልማት እና ከክልል እስከ ወረዳ የተጠናከረ የድጋፍና ቁጥጥር ስራዎች ለውጤታማ አፈጻጸሙ እንዳገዘ ተናግረዋል።

በቀጣይም ክልሉ አፈጻጸሙን በማጠናከር ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የሚያቀርበውን ወርቅ ምርት ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026