የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ባንኩ የአየር ንብረት ለውጥን ለመደገፍ ከ150 ሚሊየን ዶላር  በላይ ድጋፍ አገኘ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 29/2016(ኢዜአ)፦በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚደገፈው አረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ በአፍሪካ ቀንድ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚውል 151 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማጽደቁን የአፍሪካ ልማት ባንክ ማስታወቁን ዥንዋ ዘገበ።

በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚደገፈው ይኸው ፕሮግራም "በአፍሪካ ቀንድ ለምግብና ለኑሮ ተስማሚ የአየር ንብረት ለውጥን መገንባት" የሚለው የባንኩ ቡድን የገንዘብ ድጋፍ በጅቡቲ፣ በሶማሊያ፣ በኬኒያ፣ በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎችን ተጠቃሚ እንደሚሆኑም አመልክቷል።

የአፍሪካ ልማት ባንክን ጠቅሶ እንደዘገበው "አዲሱ የገንዘብ ድጋፍ ማኅበረሰብ ተኮርና የሥርዓተ-ፆታ መመጣጠንን የሚቋቋም መፍትሄዎችን ይደግፋል" መባሉን ዥንዋ ዘግቧል።

ዘላቂ የመሬት አስተዳደር ተግባራትን የአየር ንብረት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት፣ ታዳሽ ኃይል፣ የህብረት ስራ ማህበራት አቅም ግንባታ፣ አግሪ ቢዝነስ እና የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ተቋማት፤የብድር፣የአየር ንብረት አገልግሎት፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓቶች፣ እና የኢንሹራንስ የመረጃ ጠቋሚ ጉዳዮችን ማሻሻል የሚሉት መፍትሄዎችን እንደሚረዳ ባንኩ መግለጹን ዘገባው ጠቅሷል።

የባንኩ የግብርና እና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ዳይሬክተር ማርቲን ፍሬጌን የአፍሪካ ልማት ባንክ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ቁርጠኛ መሆኑን መግለጻቸውን ዘገባው አመልክቷል።

የአረንጓዴ የአየር ንብረት ፈንድ ድጋፍ ማሰባሰብ የአፍሪካ ልማት ባንክ ቡድን ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገርና ቀጣይነት ያለው የግብርና ሥርዓትን በአፍሪካ ቀንድ ለማሳደግ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል፣በዚህም በድራችን በጣም ተጋላጭ ከሆኑ አካባቢዎች በአንዱ የምግብ ዋስትናን ያሻሽላል ብለዋል ሲል ጠቅሷል።

ለፕሮግራሙ ከጸደቀው የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ 90 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሲሆን የ60 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ብድር መሆኑን ዥንዋ በዘገባው አመልክቷል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ በ2025 በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ተግባራዊ ማድረግ የሚጀምረው ድጋፍ እንደሚያስተዳድርና ፕሮግራሙን እንደሚቆጣጠርም ማስታወቁንም ዘገባው ጠቅሷል።

የአፍሪካ ቀንድ ከአየር ንብረት ጋር በተያያዘ ያልተስተካከለ የዝናብ ስርጭት፣ለሙቀት መጨመር፣ ለድርቅና ጎርፍ አደጋዎች ተጋላጭ መሆኑን የአፍሪካ ልማት ባንክ ማመልከቱን ዘገባው አንስቷል።

የአየር ንብረት ለውጥ ለሰው፣ ለእንስሳትና ለሰብልና በሽታዎች መጨመርና ለየመሬት መራቆትን በማባባስ ምርታማነትን እንዲቀንስ ማድረጉንም ባንኩ መግለጹን አንስቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026

<p>የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...

Feb 28, 2025

<p>የባለፉት ዓመታት ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት አሳድገዋል</p>

ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...

Feb 24, 2025