🔇Unmute
አርባምንጭ፤ ሚያዝያ 3/2018 (ኢዜአ)፦ በአርባምንጭ ከተማ ለትንሳኤ በዓል የግብርና እና ሌሎች የፍጆታ ምርቶች በስፋት ለገበያ መቅረባቸውን ሸማቾችና ነጋዴዎች ገለጹ።
ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አስተያየታቸውን የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎችና ነጋዴዎች እንደገለጹት፤ የበዓል ገበያውን ለማረጋጋት የሚያስችሉ የተለያዩ ምርቶች በበቂ ሁኔታ ቀርበዋል።
ከሸማቾቹ መካከል አቶ ግዛቸው ጊዶሌ የዘንድሮው የፋሲካ በዓል የፋብሪካና የግብርና ምርቶች በበቂ ሁኔታ የቀረቡበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በከተማው የሚገኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ በማቅረብ ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ሌላው አቶ አማኑኤል አስጨናቂ በዘንድሮው ገበያ ላይ የተወሰነ የዋጋ ጭማሪ ቢታይም፣ የምርት አቅርቦቱ አስተማማኝ በመሆኑ ሁሉም ሸማች እንደ አቅሙ መግዛት የሚችልበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
ነዋሪው ከሰንበት ገበያዎች የመገብየት ልምዱን ሊያዳብር እንደሚገባም መክረዋል።
በከተማዋ የሚገኙ የሰንበት ገበያ ማዕከላት ምርቶችን ከመደበኛው ገበያ ባነሰ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑ የብራዘርስ ሰንበት ገበያ ማዕከል የሽያጭ ባለሙያዋ ታሪኳ ወሰቶ ተናግራለች።
በተለይም ነጭና ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማቲም እንዲሁም የተለያዩ የፋብሪካ ምርቶች ከመደበኛው ገበያ በረከሰ ዋጋ ለማህበረሰቡ እየቀረቡ ነው።
የኤልያስ አየለ ሰንበት ገበያ የማዕከሉ ባለቤት አቶ ኤልያስ አየለ በበኩላቸው፤ ነዋሪው ለበዓልም ሆነ ለአዘቦት ቀናት እንዳይቸገር ጤፍ፣ በቆሎ፣ ስንዴ እና ማሽላን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ምርቶችን በስፋት እያቀረቡ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በአርባምንጭ ከተማ እየተስፋፉ የመጡት የሰንበት ገበያዎች በሸማቹና በምርት አቅራቢው መካከል ያለውን ደላላ በማስቀረት፣ በዓሉ በዝቅተኛ ወጪ እንዲከበር ትልቅ እገዛ እያደረጉ መሆኑ ተመላክቷል።
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025