የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አዲሱ የመንግስት የመሠረተ ልማት ግንባታና የቤቶች ልማት እሳቤ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ነው-ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ

Apr 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ የመንግስት የመሠረተ ልማት ግንባታና የቤቶች ልማት እሳቤ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከተሞቿን ለነዋሪዎች ምቹ፣ለኢንቨስትመንት ሳቢ እና ለቱሪዝም ተመራጭ ለማድረግ አዳዲስ የልማት ስልቶችን ስትከተል ቆይታለች።

ይህ ሀገራዊ ለውጥ በከተማ ልማት ዘርፍ መሰረታዊ ሽግግር ያመጣ ሲሆን፣ከተሞችን ከነባር መዋቅራቸው በማላቀቅ ወደ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የኢኮኖሚ ማዕከላት የመለወጥ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።


ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በከተማ ልማት፣በውበት እና በአረንጓዴ ልማት ረገድ በርካታ ተጨባጭ ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ሰፊ የእግረኛ መንገዶች፣የብስክሌት መስመር እና ማራኪ እይታ እንዲኖር የተከናወነበት ሲሆን፣ይህም ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ውብ እንዲሆኑ ከማድረጉም ባለፈ የትራፊክ ፍሰቱንና የከተማ ገጽታውን በእጅጉ ቀይሮታል።

የሀገራዊ ለውጡ አንዱ ግብ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር በዘላቂነት መፍታት ሲሆን፤ የዚሁ የለውጥ ጉዞ ውጤትና የጉባ ብስራት የሆነውን የአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ቤቶች በላይ ግንባታ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ውስጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ እውን ለማድረግ ታላቅ ዕቅድ ተይዞ ወደ ተግባር ተገብቷል።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እንደገለጹት፤ የከተማ አካባቢዎች ውድ እና በርካታ መሰረተ ልማት የሚፈስባቸው ናቸው።

ቀደም ብሎ እነዚህ ቦታዎች ከደረጃ በታች ተገንብተው ጥቅም ላይ ውለው እንደነበር አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት እነዚህ አካባቢዎች ለንግድ፣ ለመኖሪያና እና የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ዘመናዊ ግንባታዎች እየተከናወኑባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

እነዚህ ግንባታዎች ደረጃውን በጠበቀ መንገድ እየተገነቡ ከተሞችንም እየለወጡ እንደሚገኙ ጠቁመው፤አዲሱ የመንግስት የከተማ እና መሰረተ ልማት እሳቤ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን አመልክተዋል።

የመደመር መንግስት የብልፅግና ጉዞ ሊሳካ የሚችለው በሚከናወኑ የዕለት ተዕለት ስራዎች መሆኑን በግልጽ ማስቀመጡን ጠቁመዋል።

የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሳለጥ ከመንግስት ጥረት በተጨማሪ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተናግረዋል።

በጋራ በመተባበር፣አዳዲስ ፈጠራዎችን እና ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ በማዋል ይህንን ምላሽ መስጠት እንደሚቻል ገልጸዋል።

ከጉባ ብስራቶች አንዱ የሆነው የአንድ ነጥብ አምስት ሚልዮን ቤቶች ግንባታ በአምስት ዓመት ውስጥ እውን ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል።

ይህንን ለማሳካት የመንግስት የሆነው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የግል ዘርፉን በማሳተፍ ጥረቶች እንደሚደረጉ ተናግረዋል።

የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025