🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ በኢነርጂ ዘርፍ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ወደ ተግባር መግባቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብዱልፈታህ ራቢ ገለጹ።
ኢነርጂ የአንድ ሀገር የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እድገት መሰረት ሲሆን በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የኢነርጂ አቅርቦት ከኢንዱስትሪ መስፋፋት፣ ከግብርና ዘመናዊነትና ከዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው፡፡
በመሆኑም በኢነርጂ ዘርፍ እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ያለው ቁርኝት ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ወሳኝ ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን ተቋማቱ የሀገርን የኢነርጂ ዘርፍ በማዘመን በኩል የማይተካ ሚና አላቸው፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር አብዱልፈታህ ራቢ ሀገራዊ ተልዕኮውን እውን ለማድረግ በዘርፉ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራትና ምርምሮችን ለማካሄድ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በተያዘው የትምህርት ዘመን በፔትሮሊየም ኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፍ ማስተማር መጀመሩን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከኢነርጂ ዘርፍ ጋር የተያያዙ 27 የሁለተኛ ድግሪ እና 36 የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራሞች ተከፍተው ስራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
በዚህም በኢነርጂ ዘርፍ የሀገሪቱ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤታማነት ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ የትምህርት ጥራቱን ለማሳደግና ዓለምአቀፍ ልምዶችን ለመቅሰም በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ካላቸው የቻይና ዩኒቨርሲቲዎች እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጸዋል።
ለሀገሪቱ የኢነርጂ ኢንዱስትሪ የሚመጥኑ፣ በዕውቀትና በክህሎት የበለጸጉ ባለሙያዎችን በማፍራት በኩል ዩኒቨርሲቲው ግንባር ቀደም ሚና እንደሚጫወት ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026