🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ) ፦ በሀረሪ ክልል መንግስት ከወሰነው የነዳጅ ታሪፍ በላይ እንዲሁም ከግብይት ሰንሰለት ውጪ ሲሸጡ በተገኙ ሁለት ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል።
የክልሉ ንግድ ልማት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ እንደገለፁት እርምጃ የተወሰደባቸው ነዳጅ ማደያዎች መንግሥት ከወሰነው ታሪፍ በላይ በመሸጥ እንዲሁም ከመደበኛው ገበያ ውጭ በስውር ለጥቁር ገበያ ሲሸጡ በመገኘታቸው ነው።

ነዳጅ ማደያዎቹ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ተደጋጋሚ የፅሁፍና የቃል ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ቢሆንም ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንዳልቻሉም ኃላፊው አስረድተዋል።
በዚህም ማደያዎቹ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ምንም አይነት የነዳጅ ምርት እንዳይሸጡ ተደርገዋል ብለዋል።
በነዳጅ ግብይት ላይ የሚደረገው ክትትልና ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊው ጠቁመዋል ።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025