🔇Unmute
ሰቆጣ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የቡና ልማትን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ ነው።
በአሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ የመስኖ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ ደሳለኝ አዳነ እንዳሉት፤ እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ2 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በ36 ሔክታር ላይ የቡና ልማት ተከናውኗል።
በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብርም በ11 ሔክታር ላይ በኩታ ገጠም ለማልማት የሚያስችል 16 ሺህ 854 የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን ለኢዜአ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ለቡና ልማት ተስማሚ የዓየር ንብረትና ሥነ-ምኅዳር ያላቸውን አካባቢዎች የመለየትና አርሶ አደሮቹን የማዘጋጀት ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አመላክተዋል።
በዚህም 1 ሺህ 324 አርሶ አደሮች እንደሚሳተፉ ጠቁመው፤ የቡና ልማቱም በኩታ ገጠም የእርሻ ሥነ-ዘዴ ይከናወናል ብለዋል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025