🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዓመታት የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር የተጀመረው ቅንጅታዊ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን "በተቀናጀና ቀጣይነት ባለው የድጋፍ ማዕቀፍ አምራቿንና ምርታማዋን ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እንፈጥራለን" በሚል መሪ ሃሳብ ክልል አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም በወላይታ ሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በፎረሙ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሩ በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን በመቅረፍ አልሚ ባለሃብቶችን ማበረታታትና መደገፍ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በክልሉ ባለፉት ዓመታት የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከግሉ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ጋር በቅንጅት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ክልሉ ያለውን ዕምቅ የኢንቨስትመንት አቅም በመጠቀም የሰላም፣ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በተጀመረው ጥረት የግሉ ባለሀብት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም ባሉን አቅሞችና ዕድሎች ዙሪያ በመወያየት ክልሉ ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ማግኘት እንዲችል የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አፀደ አይዛ በበኩላቸው በክልሉ 82 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 1ሺህ 826 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ ገብተው በርካቶችን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።
ክልሉ ከተመሰረተ በኃላ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 536 የኢቨስትመንት ፕሮጀክቶች በኢንቨስትመንት ቦርድ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡
ፕሮጀክቶቹ ለስራ እድል ፈጠራ፣ ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ ሚና እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው በክልሉ ያለውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው ማልማት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች ተገቢው ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025