የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ላደረጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተካሄዷል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ ነው።

የክልሉ መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ስራ አጥ ዜጎችን ወደ ስራ ለማስገባት በሚደረገው ጥረት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የፋይናንስና የክህሎት ስልጠና በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

የክልሉ መንግስት ከአጋር አካላት ጋር የጀመረውን ቅንጅት በማጠናከር በዘርፉ የሚከናወነውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በበኩላቸው፤ በክልሉ በስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ልማት ዘርፍ ለተገኙ ውጤቶች የአጋር አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።


በተለይም ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በመተግበር ሂደት የክህሎት ልማት ላይ የተከናወኑ ተግባራት በዘርፉ ለተገኘው ውጤት ጉልህ ሚናን አበርክቷል ብለዋል።

የስራ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ኢንዱስትሪውን እንዲቀላቀሉ በሚደረገው ጥረት የማምረቻና መሸጫ ቦታዎችን በማዘጋጀትና የማሽነሪ ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል።


የዛሬው መድረክ ዋና ዓላማም እስካሁን ለተከናወነው ተግባር ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት ቅንጅቱን የማጠናከር ስራ ለመስራት ነው ብለዋል።

በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አጋር አካላት በተያዘው በጀት ዓመት ከ39 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስልጠና ድጋፍ ማድረጋቸውም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025