የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አጀንዳ 2063 በአፍሪካውያን ኑሮ ላይ የሚጨበጥ ለውጥ እንዲያመጣ ማድረግ ይገባል- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ 

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 23/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ሀገራት አጀንዳ 2063 ከአህጉራዊ ራዕይ ባለፈ የዜጎችን ኑሮ የሚቀይር ፕሮጀክት ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አሳሰቡ።

የአጀንዳ 2063 ትግበራ የሚከታተለው የሚኒስትሮች ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባውን በበይነ መረብ አድርጓል።


የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በዚሁ ወቅት እንዳሉት አዲሱ የህብረቱ አመራር አጀንዳ 2063 ውጤታማ ለማድረግ ከቃል የተሻገረ የፖለቲካ ቁርጠኝነትን በመላበስ አበክሮ መስራት ይገባዋል።

የአጀንዳ 2063 የ10 ዓመት የሁለተኛ ምዕራፍ የትግበራ እቅድ አህጉራዊውን ማዕቀፍ ለማፋጠን የሚያስችል ግልጽ ፍኖተ ካርታ እንዳለው አመልክተዋል።

ይሁንና አነስተኛ የፋይናንስ አቅርቦት፣ የትላልቅ ፕሮጀክቶች መጓተት እና የተቋማዊ አቅም ውስንነት የሚፈለገውን ውጤት አለማስገኘቱን ተናግረዋል።

ሊቀ መንበሩ ራዕይን ከፋይናንስ አቅርቦት፣ እቅድን የመፈጸም አቅምን ከመጨመር እና ክትትልን ከተጠያቂነት ጋር ማስተሳሰር ይገባል ነው ያሉት።

የአስተዳደር ሪፎርሞች ማጠናከር እና የፖሊሲ ማነቆዎችን ማስቀረት ቁልፍ እንደሆነም አንስተዋል።

የአፍሪካ ሀገራት ከአጀንዳ 2063ትንየአፍሪካውያን የዕለት ተዕለት ኑሮ ወደ መቀየር ምዕራፍ ለማሸጋገር በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ሊቀ መንበሩ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025