የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ክልሉ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ፈቃድ ሰጠ

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 30/2018 (ኢዜአ)፡- ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሥድስት ወራት 10 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሰጠ።

የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አባስ መሐመድ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት÷ ፈቃድ የተሰጣቸው 146 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ናቸው።

ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል 26ቱ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ያስመዘገቡ የዳያስፖራ ባለሃብቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአጠቃላይ ፈቃድ የተሰጠባቸው ዘርፎችም ግብርና፣ አገልግሎት እና ኢንዱስትሪ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቶቹ ወደ ሥራ ሲገቡ ለ21 ሺህ 679 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር ይጠበቃል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ፈቃድ ያወጡ ፕሮጀክቶች ያስመዘገቡት ካፒታል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 95 ቢሊየን ብር ብልጫ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።

በሌላ በኩል የተረከቡትን መሬት በአግባቡ ባላለሙ 40 ፕሮጀክቶች ላይ የተለያየ ደረጃ ያለው ርምጃ መወሰዱን አስረድተዋል።

በዚህም መሠረት 33 ማስጠንቀቂያ እንዲሁም ሰባት ፕሮጀክቶች ላይ ደግሞ ውልና የኢንቨስትመንት ፈቃድ የመሰረዝ ርምጃ መወሰዱን ነው ያስረዱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025