🔇Unmute
ሰቆጣ ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ከ4 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ የማልማት ስራ መጀመሩን የብሄረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
መምሪያው የ2018 የመስኖ ልማት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ አካሂዷል።
የመምሪያው ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በብሄረሰብ አስተዳደሩ የሚስተዋለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ የመስኖ ልማት ዋና አቅም ነው።
በዚህም በያዝነው የበጋ ወቅት 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት በሁለት ዙር መስኖ በማልማት ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።
በመስኖ ከሚለማው መሬት ውስጥም አንድ ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት በበጋ ስንዴ የሚሸፈን ሲሆን ቀሪው ደግሞ በሌሎች ሰብሎችና የአትክልት ምርቶች እንደሚለማ ተናግረዋል።
እስካሁን በተደረገው ጥረት ከአንድ ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው ምርታማነቱን ለማሳደግ የማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።
በብሄረሰብ አስተዳደሩ በባለፈው ዓመት በመስኖ ከለማው መሬት ላይ 810 ሺህ 637 ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025