የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል በሩብ ዓመቱ ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጬቶች ተሰራጭተዋል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በሩብ ዓመቱ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጬቶች መሰራጨታቸውን የክልሉ እንስሳትና አሣ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የዘርፉ ባለሙያ ሙላት ዳኛው ለኢዜአ እንደገለጹት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ውጤታማ ለማድረግ ለዶሮ እርባታ ተደራሽነት ትኩረት ተሰጥቷል።

ለዚህም በበጀት ዓመቱ ከ13 ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ለአርቢዎች ለማሰራጨት ታቅዶ በሩብ ዓመቱ ብቻ 2 ሚሊዮን 852ሺህ ጫጩቶችን ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል።

‎በዕቅድ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የዶሮ ጫጩቶችን የማስፈልፈል፣ የማሳደግና ለአርቢዎች የማሰራጨት ሥራ በቅንጅት እንደሚሰራም አክለዋል።


በዶሮ እርባታው ዘርፍ ከተሰማሩ አንቀሳቃሾቸ መካከል የዘምባባ ዶሮ እርባታ ማህበር ሊቀመንበር ወጣት ዮሴፍ ፈቃዱ እንደገለጸው፣ ማህበሩ ሰባት አባላት እንዳሉትና ከመንግስት በተሰጣቸው መስርያ ቦታ 6ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ላይ ናቸው።

በአሁኑ ወቅት 45 ቀን የሞላቸውን እንቁላል ጣይ ቄብ ዶሮዎችን ለአርቢዎች ለማሰራጨት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጠቅሷል።

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የአንድ ቀን ጫጩቶችን አሳድጎ ለአርቢዎች ማሰራጨት ውጤታማ እንደሚያደርግ የገለፀው ደግሞ በባህር ዳር ከተማ በዘርፉ የተሰማራው ወጣት ማስተዋል አያልነህ ነው።

ሁለት ሆነው በመደራጀት በዚህ ሥራ መሰማራታቸውን ጠቁሞ በዓመት እስከ 75ሺህ ጫጩቶችን አሳድገው ለአርቢዎች በማሰራጨት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን ተናግሯል።

ያለባቸውን የቦታ ችግር የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ከፈታላቸው ተጨማሪ ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ለአርቢዎች በማሰራጨት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እንደሚሰሩም ገልጿል።

በክልሉ ባለፈው ዓመት ስድስት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን የአንድ ቀን ጫጩቶችን በማስፈልፈል ማሰራጨታቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025