🔇Unmute
ጎንደር፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ):-የጎንደር ከተማ አስተዳደር በስሩ ባሉ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች የገጠር ኮሪደር ልማትን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተናገሩ፡፡
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ቻላቸው ዳኘው ለኢዜአ እንደገለጹት የገጠር ኮሪደር ልማቱ የሚተገበረው በአዘዞ ተክለሃይማኖት እና ሳቢያ ሳይና በተባሉ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች ነው።
በአሁኑ ወቅትም የኮሪደር ልማቱን የሚመሩ ኮሚቴዎችን ከማቋቋም ባለፈ ከሚተገበርባቸው ቀበሌዎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት በማድረግ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።
የኮሪደር ልማቱን ለማስተግበር የሚያስችል ዕቅድ በማዘጋጀት በተያዘው በጀት ዓመት ሥራውን ለማከናወን እየተሰራ መሆኑንም አቶ ቻላቸው ተናግረዋል፡፡
በልማቱም ሞዴል የአርሶ አደር መኖሪያ ቤቶች፣ የመንገድ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና በታዳሽ ሃይል ላይ የተመሰረቱ የኢነርጂ አማራጮች እንደሚተገበሩ ነው የገለጹት።
የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየር ዘመናዊ አኗኗርን የሚያጎናጽፍና አዲስ የአስተሳሰብ እይታን የሚያሰፋ በመሆኑ ለሀገራዊ እድገት መሰረት መሆኑን ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ እየተገነባ ያለው ሁለተኛው ምዕራፍ የከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑ ተመልክቷል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025