የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያረጋገጥንበት ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ከማድረግ ባሻገር ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አመራር አባላት ገለጹ።

የኢንስቲትዩት አመራር አባላት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከበደ ቶሎሳ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ታላቁ የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የብዙ ዘመን ምኞት እውን ያደረገ ፕሮጀክት ነው።

ታላቁ ህዳሴ ግድብ መላው ኢትዮጵያውያንን ወደ ብርሀን ያመጣ የድል ብስራት መሆኑን ጠቁመው፤ አገሪቷ ከድህነት የምትወጣበትን አቅጣጫ ያሳየ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢንስቲትዩቱ ለግድቡ በተለያዩ መንገዶች የቴክኖሎጂ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፤ ዲጂታላይዜሽንን ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰው ሀብት ልማት እና አስተዳደር ዳይሬክተር ግርማቸው ጌቱ በበኩላቸው፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ የያዘቻቸውን ስትራቴጂያዊ ግቦች የሚያሳካ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።

እንዲሁም በራስ አቅም መልማት እና ማደግ እንደሚቻል ትምህርት የሰጠ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።

ታላቁ ህዳሴ ግድቡ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይም ሌሎች ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ከማድረግ ባሻገር ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።

አብዛኛው ቴክኖሎጂ የኤሌክትሪክ ሀይል እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ቀጣይ በመንግስት የተያዙ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ከመደገፍ አኳያም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025