የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች በፍራፍሬ ልማት መሠማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው ነው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ ሐምሌ 16/2017(ኢዜአ)፡-በፍራፍሬ ልማት መሠማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው መምጣቱን የሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ317 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ እንደታቸለ አስታውቋል።


በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ ቡሆሮ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ተገኘ ወርቁ ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከማንጎና ፓፓያ ምርት ሽያጭ ከ87 ሺህ ብር በላይ አግኝተዋል።

በአሁኑ ወቅትም ተጨማሪ የማንጎና ፓፓያ ምርቶችን ለገበያ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም ልማቱን በማስፋፋተ በሚያገኙት ገቢ ወደንግድ ስራ ለመሰማራት ማቀደቻውን ተናግረዋል።

በዞኑ ጉባላፍቶ ወረዳ የአላውሃ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጎበዜ በላይ በበኩላቸው የማንጎ፣ ፓፓያና ሙዝ ምርት ለገበያ በማቅረብ በበጀት ዓመቱ ከ45 ሺህ ብር በላይ ገቢ መግኘታቸውን ተናግረዋል።

ከፍራፍሬ ልማቱ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን ከማስተዳደር ባለፈ የኢኮኖሚ አቅማቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።


በሰሜን ወሎ ዞን በመስኖና በመደበኛ እርሻ በ1ሺህ 655 ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ መልማቱን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ ቡድን መሪ አቶ አለባቸው መራዊ ናቸው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመስኖ ከለማው ፍራፍሬ 317 ሺህ 220 ኩንታል ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።

በልማቱም 82 ሺህ 750 አርሶ አደሮች በመሳተፍ ማንጎ፣ አቡካዶ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ አፕል፣ ብርቱካንና ሌሎች ፍራፍሬዎችን በመስኖ ማልማታቸውን ተናግረዋል።

አርሶ አደሮቹ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የግብርና ቴክኖሎጂ ከመጠቀም በተጨማሪ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን እያለሙ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ከመምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በ2016 በጀት ዓመት በዞኑ ከ310 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025