የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በ2018 በጀት ዓመት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ይከናወናሉ-አቶ አሻድሊ ሀሰን

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት እንደሚከናወኑ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።

ለሁለት ቀናት በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክልሉ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።


በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፤ በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተሻለ አፈጻጸም በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ተጨባጭ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል።

በክልሉ የገቢ አማራጭችን በማስፋት እና የአሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን የመንግሥትን የልማት ወጪ ፍላጎት ለመሸፈን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የገቢ አሰባሰብ ላይ የታየው መሻሻል የልማት ስራዎችን ለማከናወን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው ያሉት አቶ አሻድሊ ባለሃብቶችን እና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን መታቀዱን ገልጸዋል።

በአሶሳ ከተማ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ወደ ሌሎች ከተሞች በማስፋት፣ የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት በማልማት እና በመጠቀም የክልሉን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የ2018 በጀት ዓመት እንደ ሀገር ትልልቅ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ የሚገቡበት መሆኑን ገልፀው ይህም ሀገራዊ ብልጽግና የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ እንደሚሆንም ተናግረዋል።


በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በበኩላቸው ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጀመሩ ተግባራትን በሁሉም ወረዳዎች የማስፋት ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመላክተዋል።



አመራሩ የተያዙ ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት ለመስራት ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበትም አቶ ኢሳቅ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025