
አሶሳ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት እንደሚከናወኑ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
ለሁለት ቀናት በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክልሉ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፤ በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተሻለ አፈጻጸም በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ተጨባጭ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል።
በክልሉ የገቢ አማራጭችን በማስፋት እና የአሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን የመንግሥትን የልማት ወጪ ፍላጎት ለመሸፈን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የገቢ አሰባሰብ ላይ የታየው መሻሻል የልማት ስራዎችን ለማከናወን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው ያሉት አቶ አሻድሊ ባለሃብቶችን እና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን መታቀዱን ገልጸዋል።
በአሶሳ ከተማ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ወደ ሌሎች ከተሞች በማስፋት፣ የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት በማልማት እና በመጠቀም የክልሉን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የ2018 በጀት ዓመት እንደ ሀገር ትልልቅ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ የሚገቡበት መሆኑን ገልፀው ይህም ሀገራዊ ብልጽግና የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ እንደሚሆንም ተናግረዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በበኩላቸው ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጀመሩ ተግባራትን በሁሉም ወረዳዎች የማስፋት ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመላክተዋል።
አመራሩ የተያዙ ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት ለመስራት ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበትም አቶ ኢሳቅ አሳስበዋል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025