የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታችንን በወቅቱ ለመወጣት እያገዘን ነው-በሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች

Jul 15, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜያቸውን ከመቆጠብና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታቸውን በወቅቱ ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን የሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች ገለጹ።

የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን በበኩሉ በሰባት ቀናት ውስጥ በክልሉ ከሚገኙ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል።

በሲዳማ ክልል ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች በቴክኖሎጂ ታግዘው በቴሌ ብር ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ሲሆን ዘመናዊ አሰራሩ ጊዜንና እንግልትን ከመቀነስ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በክልሉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ቦርጂ በማማከር አገልግሎት ከሚያገኙት ገቢ የሚጠበቅባቸውን ግብር በቴሌ ብር መክፈላቸው ጊዜያቸውን እንደቆጠበላቸው ገልጸዋል።


ግብርን በወቅቱ መክፈል መንግስት ለሚያከናውነው የልማት ሥራ አጋዥ መሆኑን ጠቁመው፣ የግብር አሰባሰቡ መዘመኑ ግብር ከፋዩ በወቅቱ የሚጠበቅበትን ለመወጣት እያስቻለው መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ ይርጋለም ከተማ የሚኖረት አቶ ምትኩ ጸጋዬ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መዘርጋቱ ግብራቸውን በቴሌ ብር ለመክፈልና ጊዜያቸውን ለመቆጠብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡


ግብር ለሃገር እድገት የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ምትኩ የሚጠበቅባቸውን ግብር በታማኝነት እንደከፈሉና ሌሎችም ሃላፊነታቸውን በወቅቱ መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታና ለልማት የሚደረግ አስተዋጽኦ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ የወንዶገነት ከተማ ነዋሪው አቶ ማሞ ቱላ ናቸው።


በሚኖሩበት ከተማ እየተከናወነ ያለው ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ ግዴታቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረው፣ "አገልግሎቱ በቴሌ ብር መታገዙ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልትን አስቀርቶልኛል" ብለዋል።

የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርና የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አወሳሰንና የገቢ አሰባሰብ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በክልሉ ከ35ሺህ 816 በላይ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ይገኛሉ፡፡

ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም በሰባት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር ተገብቷል ብለዋል።


በክልሉ ከሚገኙ 45 መዋቅሮች በ31ዱ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ በቴሌብር ታግዞ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ሥርአት መዘርጋቱ ለግብር ከፋዮች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ህገወጥ ተግባራትን ለመከላከል እያገዘ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመዘርጋት ግብር ከፋዮች ንግድ ፈቃዳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሌሎች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱ እንግልት ያስቀረ፣ ጊዜና ጉልበት የቆጠበ ነው ሲሉም ምክትል ዳይሬክተሯ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025