የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዞኑ የህብረት ስራ ማህበራትን አቅም በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው

Jul 14, 2025

IDOPRESS

ደብረማርቆስ ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን የህብረት ስራ ማህበራትን አቅም በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ 17 የእርሻ ትራክተሮችና ኮምባይነሮችን ለሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራትና ባለሀብቶች ዛሬ አስረክቧል።


የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ እንዳሉት በዞኑ የህብረት ስራ ማህበራትን አቅም በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።

የምርታማነት ማደግ የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ከማሻሻል ባለፈ ገበያን በማረጋጋት የዋጋ ንረትን በመቀነስ ረገድ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል።

የዞኑን የምርታማነት አሁን ካለበት ለማሳደግ የሜካናይዜሽን ግብርናን ማስፋፋትና ተደራሽ ማድረግ የህልውና ጉዳይ ሊሆን ይገባል ያሉት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበበ መኮንን ናቸው።

ለዚህም የክልሉ መንግስት ባደረገው ድጎማ ዘጠኝ ትራክተሮችና ስድስት ኮምባይነሮችን ለሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ድጋፍ ማድረግ እንደቻለም ተናግረዋል።


በተጨማሪም በረጅም ጊዜ ክፍያ ለሁለት ባለሀብቶች ሁለት ትራክተሮች ቀርበው ርክክብ መደረጉን ገልጸዋል።

የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ኤጀንሲ አማካሪ አቶ ሃይለ ልኡል ተስፋ በበኩላቸው የሜካናይዜሽን ግብርና ተደራሽነት እንዲሰፋ አልሚ ባለሃብቶችን ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡ እና ብድር እንዲያገኙ የሚደረገው ጥረት እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት በራሳቸው አቅም የሜካናይዜሽን እርሻን እንዲያስፋፉ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግላቸውም ገልፀዋል።

በእነማይ ወረዳ የልምየት የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበር አባል አርሶ አደር ብርቄ ጸጋዬ እንዳሉት ''የሜካናይዜሽን አቅርቦት ድጋፍ መደረጉ በስራችን እንድንበረታ የሚያደርግ ነው'' ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ሜካናይዜሽን ባለመኖሩ በባህላዊ አስተራረስና የምርት አሰባሰብ ጊዜያቸውን ያባክኑ እንደነበር አስታውሰዋል።



አሁን ግን በአካባቢው የሜካናይዜሽን እርሻ መጀመሩ የአርሶ አደሩን ችግር ያቃልላል የሚል ተስፋ ማሳደሩንም አርሶ አደር ብርቄ ተናግረዋል።

በዞኑ ለምርት ዘመኑ ከ642 ሺህ ሄክታር በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም ከ25 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝም ተገልጿል።

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሰብል ከሚሸፈነው መሬት 58 በመቶ የሚሆነው በትራክተር ለመታረስ ምቹ መሆኑም ከዞኑ ግብርና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025