የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ለገጠር መንገድ ተደራሽነት ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Jul 14, 2025

IDOPRESS

ወላይታ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ ለገጠር መንገድ ተደራሽነት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወላይታ ዞን ዳሞት ጋሌ ወረዳ ከ36 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባውን 20 ኪሎ ሜትር የገጠር ተደራሽ መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት ገጠርን ከከተማ የሚያገናኝ መንገድ መገንባት አርሶ አደሩ የግብርና ምርቱን ለገበያ ለማቅረብና የፋብሪካ ሸቀጦችን በቀላሉ ወደ አካባቢው ማስግባት የሚያስችለው ነው።

ይህም የአርሶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ያሉት አቶ ጥላሁን፣ የክልሉ መንግስት የህዝብን የመንገድ ተደራሽነት ጥያቄ ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አመልክትዋል።

ዛሬ የተመረቀው መንገድ ለእዚህ አንድ ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ ህብረተሰቡ የተገነቡ መንገዶች ለረጅም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል።


የመንገዶቹ መገንባት የአርሶ አደሮችን ማህበራዊ ግንኙነት እንደሚያቀላጥፍ የገለጹት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው።

የመንገዶቹ መጠናቀቅ የግብርና ውጤቶችን በቀላሉ ወደ ከተማ ለመውሰድ እንዲሁም ነፍሰጡሮችን ጨምሮ ህሙማንን ወደ ጤና ተቋማት በፍጥነት ለማድረስ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።

የመንገዶቹ ግንባታ በታለመለት የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

መንገዱ ከቦዲቲ ከተማ ተነስቶ ቦሎሶ ሶሬ ወረዳን በማቋረጥ ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ ከሚወስድ የአስፖልት መንገድ ጋር እንደሚያገናኝ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ርዕሰ መስተደድር ጥላሁን ከበደ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) እንዲሁም የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025