አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ በሁሉም የአገሪቷ አካባቢዎች የተገነቡና የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ ከ20ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብስባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት የመንግስት የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
የምክር ቤቱ አባላት በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ዲፕሎማሲ እና በሌሎች ጉዳዮች ጥያቄና አስተያየታቸውን አቅርበዋል።
የኮሪደር ልማትን በሚመለከት በሁሉም የአገሪቷ ከተሞች የሚካሄዱ ልማቶች አሳታፊነት ላይ ከምክር ቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መንግስት ከኮሪደር በተጨማሪ በርካታ የልማት ስራዎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ መካከል መንግስት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሻሉና በማህበረሰቡ ሲጠየቁ የቆዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት ረገድ በቁርጠኝነት እየሰራ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት እስከ ነሃሴ መጨረሻ ድረስ የሚመረቁ ከ20 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቶቹ የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ የጤና ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶችና መሰል የመሰረተ ልማት ስራዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025