የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በመዲናዋ የገበያ ማዕከላት መስፋፋት ምርቶችን በበቂ እና በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት አስችሎናል- ሸማቾች

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የገበያ ማዕከላት መስፋፋት ምርቶችን በበቂ እና በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እያስቻላቸው መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ሸማቾች ገለጹ።


በመዲናዋ የተገነቡ የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን እንደ ድልድይ ሆኖ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡

ለማሳያነትም ኢዜአ ከእነዚህ ማዕከላት አንዱ በሆነው የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከልን እንቅስቃሴ ቅኝት አድርጓል።

ሸማቾች እንደሚሉትም በማዕከሉ በተመጣጣኝ ዋጋ የአትክልትና ፍራፍሬ እና የሰብል ምርቶችን እየገዙ እና እየተጠቀሙ መሆኑን አንስተዋል።

በማዕከሉ ስትገበያይ ያገኘናት ሸማች አበበች አሰፋ እንደገለጸችው ፤ በማዕከሉ ሁሉንም አይነት አትክልትና ፍራፍሬ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመተች መሆኑን በመግለጽ፤ በዋጋ ተመጣጣኝ የሆነ አገልግሎት እንዳገኘች ትናገራለች፡፡

ሌላው ያነጋገርነው ሸማች ተማም ጀማል በበኩሉ፤ ለእኛ ለሸማቾች መንግስት በየአቅራቢያችን በገነባቸው ማዕከላት አትክልትና ፍራፍሬዎችና የሰብል ምርቶችን በአቅራቢያችን በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛት መቻላችን እፎይታ ሰጥቶናል ነው ያለው፡፡


የማዕከሉ መኖር ውጪ ላይ ካለው ገበያ ሰፊ ልዩነት እንዳለውና አቅማችንን ባማከለ ዋጋ እየተገበያየን ነው ያለችው ደግሞ የምስራች አባይነህ ናት፡፡


በማዕከሉ ያነጋገርናቸው አምራቾች መካከል አቶ ተስፉ ወጂ እንዳሉት፤የገበያ ማእከላት መኖራቸው የግብይቱን ሰንሰለት በማሳጠር ምርቶቻቸውን ለተጠቃሚ ለማድረስ እድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


የሰብል ምርቶችን ጤፍ ከ10ሺህ ብር ጀምሮ፣ ሽንኩርት ከ35 ብር ጀምሮ በመሸጥ በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እየሸጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ሌላው ያነጋገርናቸው አምራች አቶ ደረጄ ጋሪ በበኩላቸው ምርቶችን ውጭ ካለው ገበያ እስከ ሃያ ፐርሰንት ቅናሽ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡


በላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል ዋና ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ከማል ሃጂ ሰኢድ እንዳሉት ፤ የገበያ ማዕከሉ መገንባት ለሸማችና ለአምራቹ ግንኙነት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ፍስሀ ጥበቡ ቢሮው ገበያ ለማረጋጋት የቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ከሁሉም የሃገሪቱ አካባቢዎች ምርቶች እንዲገቡ እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025