አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት በየአካባቢው ያሉ ሀብቶችን በማልማት ያከናወናቸው ተግባራት ሀገራዊ ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል ያመላከተ ነው ሲሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ገለጹ።
በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ከተማዋን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል የሚያደርጋት መሆኑን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮቹ አክለው ተናግረዋል።
የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም የገበታ ለትውልድ አካል የሆነውንና በግንባታ ሥራ ላይ የሚገኘውን የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ፕሮጀክት፣ የኮሪደር ልማት፣ የአርባምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም፣ የአዞ ራንች፣ አርባምንጮችንና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡት መካከል የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ነፃነት ጣሰው እንዳሉት፤ በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው የተከናወኑ የልማት ተግባራት ሀገር እምቅ ተፈጥሯዊ ሀብቷን በመጠቀም የልማት ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ያመላክታል።
የልማት ሥራዎቹ እንደሀገር ለተጀመሩ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ተጨማሪ አቅም የሚሆኑ ናቸው ብለዋል።
በተለይ በገበታ ለትውልድ እየተገነባ ያለው የአርባምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት ከተማዋን የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከል ያደርጋታል ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል።
ፓርቲያቸው እንደሀገር በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ከመንግሥት ጋር በትብብር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
የትንሳኤ ሰብዓ እንደርታ ፓርቲ ሊቀ መንበር ከበደ አሰፋ በበኩላቸው፤ መንግስት በየአካባቢው መጪውን ትውልድ ታሳቢ አድርጎ እየሰራቸው ያሉ ሥራዎች አስደናቂ ናቸው ብለዋል።
እነዚህ ሥራዎች የተሻለች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚቻል የሚያረጋግጥ እንደሆነም ተናግረዋል።
የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀ መንበር ግራኝ ጉደታ በበኩላቸው፤ መንግስት የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ እያከናወነ ያለው የልማት ሥራዎች አበረታች ናቸው።
የሀገርንና የዜጎችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ሳሙኤል ብርሃኑ እንደተናገሩት፤ የተመለከቷቸው ስራዎች ሀገራዊ ልማትን የሚያመላክቱ ናቸው።
የቅማንት ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀ መንበር ተገኑ ደረጀ በበኩላቸው፤ የልማት ሥራዎች ሁለንተናዊ ልማት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ከመንግሥት ጋር በትብብር እንሰራለን ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025