አዲስ አበባ፤ሰኔ 11/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የልማት አጀንዳዎችን ከብሔራዊ እቅዶች ጋር አጣምራ መተግበሯን አጠናክራ እንደምትቀጥል የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩማር አባተ ገለጹ።
ላላፉት ሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካ የግምገማ ማህበር 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ተጠናቋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩማር አባተ እንደተናገሩት፤ የተካሄደው መርሃ ግብር እንግዶችን በማስተናገድና ኹነቶችን በማካሄድ ስኬታማ ነበር።
የምዘና ስርዓትን ለማጠናከር የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ለመስጠት፣ የአገራት ልምድና ተሞክሮ ለመለዋወጥና ትብብርን ለማጠናከር የተያዘውን ግብ ለማሳካት እንደተቻለም አብራርተዋል።
አገራት እንደየነባራዊ ሁኔታቸው የሚከተሉትን የምዘና ስርዓት በመድረኩ ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን፤ ኢትዮጵያም ጠንካራ የክትትልና ግምገማ ስርዓትን ለመዘርጋት ያከናወነቻቸውን ተግባራት ማቅረቧን ገልጸዋል።
አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የልማት እቅዶችን ከብሔራዊ እቅዶቿ ጋር በማጣመርና የትግበራ ሂደታቸውን ሪፖርት፣ ክትትልና ግምገማ በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ እየተገበረች የምትገኘው የ10 ዓመት የልማት እቅድ እና አጀንዳ 2063 የዘላቂ ልማት ግቦችን አጣምሮ የያዘ መሆኑን በማስታወስ፤ በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
በአገር ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔና ሪፎርም ማህበረሰብን ተጠቃሚ ማድረጉን ለማወቅ ጠንካራ የክትትልና ምዘና ስርዓት ወሳኝ በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ ይገኛልም ነው ያሉት።
የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ተወካይ አምባሳደር ሞሃመድ ኢልአሚኒ በበኩላቸው፤ በአህጉሪቷ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔ በመስጠት እንዲሁም አፈጻጸሙን ክትትል በማድረግ ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የአፍሪካ የግምገማ ማህበር በአጀንዳ 2063 ትግበራ በትብብር መስራቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀው፤ አገራት ለአቅም ግንባታ ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል።
የአፍሪካ ግምገማ ማህበር ፕሬዝዳንት ሚቼ ኦዲራጎ በበኩላቸው፤ ባለፉት ሶስት ቀናት በአፍሪካ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ውሳኔ መስጠት የሚያስችል የግምገማ ስርዓትንና ትብብርን የሚያጠናክሩ ኹነቶች መካሄዳቸውን ገልጸዋል።
አንድነቷ የተጠናከረና በምጣኔ ሃብት የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ በዘላቂ ልማት ግቦችና አጀንዳ 2063 ለሚተገበሩ የልማት መርሃ ግብሮች ማህበሩ ከአገራት ጋር በትብብር የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በአፍሪካ የግምገማ ማህበር 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ ከአፍሪካ እና ሌሎች የዓለም አገራት የተውጣጡ ባለሙያዎች፣ ምሁራን፣ ፖሊሲ አውጭዎችና ከ300 በላይ እንግዶች ተሳትፈዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025