
አዳማ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።
የአሰላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ስሜ ፀጋዬ ለኢዜአ እንደገለፁት የከተማዋን ነዋሪ የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው።
በዚህም በከተማዋ የኮሪደር ልማት፣ መናኸሪያ፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትና የመዝናኛ ማዕከላት ግንባታ እንዲሁም የወንዝ ዳርቻዎችን ፅዱ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የከተማዋን እድገት በማቀላጠፍ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ ያለመ የመጀመሪያው ዙር 25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መገንባቱንም አስረድተዋል።
ከሁለተኛው ዙር የ16 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ውስጥም የ2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት ግንባታ በቀጣዩ ወር እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል።
የአሰላ ከተማን ከሚያቋርጡ አምስቱ ወንዞች በሁለቱ ላይ የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም በከተማ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የዶሮና ወተት ላሞች እርባታ ማዕከላት ተገንብተው መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።
በከተማዋ ለተመዘገበው የልማት ውጤት ባለሃብቶችን ጨምሮ ህብረተሰቡ በሁሉም መስክ እያደረጉ ላለው ተሳትፎ ከንቲባው አመስግነዋል።
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025