የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ ነው

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።

የአሰላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ስሜ ፀጋዬ ለኢዜአ እንደገለፁት የከተማዋን ነዋሪ የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በከተማዋ የኮሪደር ልማት፣ መናኸሪያ፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትና የመዝናኛ ማዕከላት ግንባታ እንዲሁም የወንዝ ዳርቻዎችን ፅዱ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማዋን እድገት በማቀላጠፍ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ ያለመ የመጀመሪያው ዙር 25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መገንባቱንም አስረድተዋል።

ከሁለተኛው ዙር የ16 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ውስጥም የ2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት ግንባታ በቀጣዩ ወር እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል።

የአሰላ ከተማን ከሚያቋርጡ አምስቱ ወንዞች በሁለቱ ላይ የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም በከተማ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የዶሮና ወተት ላሞች እርባታ ማዕከላት ተገንብተው መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

በከተማዋ ለተመዘገበው የልማት ውጤት ባለሃብቶችን ጨምሮ ህብረተሰቡ በሁሉም መስክ እያደረጉ ላለው ተሳትፎ ከንቲባው አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025