የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በጅማ ከተማ 47 የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኑ

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ 47 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የጅማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር እንዳሉት፥ አስተዳደሩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ ነው፡፡

ፕሮጀክቶቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያግዙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የግንባታ ስራቸው ከተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል ሼዶች፣ የኢንዱስትሪ ማእከሎች፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና የኮሪደር ልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡

በመንግስት በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ እነዚሁ የልማት ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደታቸውም ከ12 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን አመልክተዋል፡፡

አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ኪሩቤል ታረቀኝ በሰጠው አስተያየት በከተማዋ በኮሪደርና በሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግሯል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ ልማት ስራዎች ከተማዋን ውብና ሳቢ እንድትሆን ከማድረግ ባለፈ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ጋሊ አባ ወሊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025