
ጅማ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ 47 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የጅማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር እንዳሉት፥ አስተዳደሩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ ነው፡፡
ፕሮጀክቶቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያግዙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የግንባታ ስራቸው ከተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል ሼዶች፣ የኢንዱስትሪ ማእከሎች፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና የኮሪደር ልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡
በመንግስት በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ እነዚሁ የልማት ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደታቸውም ከ12 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን አመልክተዋል፡፡
አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ኪሩቤል ታረቀኝ በሰጠው አስተያየት በከተማዋ በኮሪደርና በሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግሯል፡፡
በከተማ አስተዳደሩ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ ልማት ስራዎች ከተማዋን ውብና ሳቢ እንድትሆን ከማድረግ ባለፈ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ጋሊ አባ ወሊ ናቸው።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025