የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ጉባኤው የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን የዲጂታል መታወቂያ ትግበራ ልምድ ለመቅሰም ጥያቄ ያቀረቡበት ነው - ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም

May 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2017(ኢዜአ)፦ አይ ዲ ፎር አፍሪካ ጉባኤ የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ዕውቀት አልምታ ከተገበረችው የዲጂታል መታወቂያ ልምድ ለመቅሰም ጥያቄ ማቅረባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያሥላሴ ገለፁ።

ለአራት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው አይ ዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ተጠናቋል።


በጉባኤው የተለያዩ ሀገራት በዲጂታል ማንነትና መሰረተ ልማት ግንባታ ያላቸውን ተሞኮሮ ያካፈሉባቸው የፖናል ውይይቶችና ባዛሮች መካሄዳቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያም በሀገር በቀል ዕውቀት በታገዘ ቴክኖሎጂ ይፋ ያደረገችው ዲጂታል መታወቂያ የበርካታ አፍሪካ ሀገራትን ቀልብ ስቧል።


የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያሥላሴ የጉባኤውን መጠናቀቅ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ሀገር በቀል ዕውቀትን ተጠቅማ ያለማችው የዲጂታል መታወቂያ ቴክኖሎጂ ከበርካታ ሀገራት አድናቆት እንደተቸረው ተናግረዋል።

በዚህም በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ በዲጂታል መታወቂያ ያካበተችውን የቴክኒክና የዕውቀት ድጋፍ መጠየቃቸውንና ኢትዮጵያም ከጉባኤው ተሳታፊ ሀገራት ልምዶች መቅሰሟን ገልጸዋል።

የአይ ዲ ፎር አፍሪካ መስራችና ሊቀመንበር ጆሴፍ አቲክ(ዶ/ር) በበኩላቸው ጉባኤው የአፍሪካን የዲጂታል ሽግግር ስኬትና ቀሪ ስራዎች ላይ ባለድርሻ አካላት በስፋት መምከራቸውን ተናግረዋል።


በአፍሪካ የዲጂታል ማንነት ግንባታ እያደገ መምጣቱን ገልፀው፤ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የተሻለ አፈፃፀም ማሳየቷን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት ያከናወናቸው ተግባራት ለዲጂታል ሽግግር የሰጠውን ትኩረት ያመላክታል ሲሉም ገልጸዋል።

አይ ዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ከሁለት ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገራት ተሳታፊዎች የታደሙበት ነበር።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025