
አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ምህዳርን የሚያጠናክሩ ቁልፍ የዲጅታል መሰረተ ልማቶችን መገንባቷን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ገለጹ።
በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ ተከፍቷል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በዚሁ ወቅት፥ቴክኖሎጂ የሁሉ ነገር መሰረት እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታውን በቅጡ በመገንዘብና ቴክኖሎጂ ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት ያለውን ፋይዳ በመረዳት ዲጂታል መሰረተ ልማትን እያስፋፋች ነው ብለዋል።
ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ፣የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ የሥልጠና ኢኒሼቲቭ እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል የማስገባት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አንስተዋል።
የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ቁልፍ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሯ፥ በስማርት ሲቲ ግንባታም ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባትና አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ቴክኖሎጂ የማይተካ ሚና እንዳለውና ይህን የበለጠ ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የሳይበር ደህንነት ካውንስል ሊቀመንበር መሃመድ አልኩዋቲ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ቴክኖሎጂ ዓለምን የመቀየር ትልቅ አቅም እንዳለው አንስተዋል።
የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የብሄራዊ ደህንነትን ሉዓላዊነት ማረጋገጥ መሆኑን ጠቅሰው፥ በዚህ ላይ ሀገራት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
ከቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የሳይበር ደህንነት ስጋቶችን ለመቀነስ ትብብርን ማጠናከርና ተለዋዋጭ የሳይበር ደህንነት ስጋትን ታሳቢ ያደረገ አቅም መገንባት ወሳኝ እንደሆነም ጠቁመዋል።
የቴክኖሎጂ ኤክስፖው እስከ ግንቦት 10/2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የበርካታ ሀገራት ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችና ከአስር ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እየተሳተፉበት ነው።
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025