
ወልቂጤ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የም ዞን ከ87 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የኮሾ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ተገለፀ።
ፕሮጀክቱን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማእረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትራንስፖርት እና መንገድ ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር ) በይፋ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
የመስኖ ፕሮጀክቱ የአርሶ አደሮችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግና ገበያ በማረጋጋት ረገድ ያለው ፋይዳ ከፍ ያለ መሆኑም ተገልጿል።
በክልሉ የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ካሳዬ ተክሌ፥ የመስኖ ፕሮጀክቱ ግንባታ በሳጃ ዙሪያ ወረዳ ዲቻ ቀበሌ በ2016 ዓ/ም አጋማሽ እንደተጀመረ ገልፀዋል።
በ87 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክቱ 600 የቤተሰብ መሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልፀው፥ ለእንስሳት የመጠጥ ውሃ የሚሆን ቦታ ተካቶበት መገንባቱን ተናግረዋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይም የክልሉና የዞኑ አመራር አባላት እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025