የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዞኑ ከ167 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

May 7, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ )፦በምስራቅ ቦረና ዞን በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከ167 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡


በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ በዞኑ በየዓመቱ ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ መጨረሻ የበልግ ወቅት እንደሆነ ገልጸው፤ በዘንድሮ የበልግ እርሻ 158 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ከእቅዱ በላይ መከናወኑን ተናግረዋል።


በዚህም በዞኑ 8 ወረዳዎች 167 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብል ዓይነቶች በዘር መሸፈኑን አስታውቀዋል፡፡


ከዚህ ውስጥ 60 ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት በስንዴ ምርጥ ዘር የተሸፈነ ሲሆን ከዚህም ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡


በዞኑ በበልግ ወቅት በብዘት ከተዘሩት ዋና ዋና የሰብል ዓይነቶች ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ቦለቄ፤ ሰሊጥ እና ማሾ መሆኑን ጠቅሰው በአጠቃላይ በዘንድሮ የበልግ ወቅት ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡


በበልግ አዝመራው ከ147 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች በልማቱ መሳተፋቸውንም ገልጸዋል፡፡


በጽህፈት ቤቱ የግብዓት አቅርቦትና ስርጭት ባለሙያ አቶ ገመዳ ሀሰን በዞኑ በበልግ አዝመራው 41 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቁመዋል፡፡


እንዲሁም ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ከ14 ሺህ ኩንታል በላይ የምርጥ ዘር ዓይነቶች ጥቅም ላይ መዋሉንም ተናግረዋል።


ምርታማነትን የሚጨምሩ አዳዲስ የግብርና ሜካናይዜሽን አሰራሮች በመመቻቸታቸው ከዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከፍተኛ ምርት ይጠበቃል ብለዋል፡፡


ከአዳዲስ አሰራሮቹ መካከል የእርሻ ትራክተር አቅርቦት፣ የኩታ ገጠም አስተራረስ፣ የግብዓት አቅርቦት እና የታረሰ መሬት ብዛት ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025