የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢሉ አባቦር ዞን 1 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታ እየተከናወነ ነው

Apr 27, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ሚያዝያ 18/2017 (ኢዜአ)፦በኢሉ አባቦር ዞን 1 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።


የኢሉ አባቦር ዞን መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ደመቁ ተረፈ እንዳሉት፥ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታው በሁለት ወረዳዎች እየተከናወነ ነው።


የክልሉ መንግስት 'ፊና' በተሰኘ ፕሮጀክት ውኃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች ግንባታ እያካሄደ ሲሆን በዞኑ በግንባታ ላይ የሚገኙ ግድቦችም የዚሁ አካል ናቸው ብለዋል።


የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ የአካባቢው አርሶ አደሮችን የማምረት አቅም በማሳደግ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው እንደሆነ ገልጸዋል።


በሁለቱ ወረዳዎች 4 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚችሉት እነዚሁ ግድቦች ግንባታቸው በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው እየተከናወነ የሚገኘው ብለዋል።


ግድቦቹ በሚገነቡበት አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮችም የመስኖ ግድቦቹ ከክረምት ባለፈ በበጋ ወራት ተጨማሪ የማምረት አቅም እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል።


አርሶ አደር አበበ ሀብተወልድ ፕሮጀክቶቹ በአካባቢያቸው የሚገኘውን ወንዝ በግብርና ስራቸው ላይ በመጠቀም ክረምትና በጋ ማምረት የሚያስችለን ነው ብለዋል።


በዚህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ወደስራ ሲገባ በዝናብ ወቅት ብቻ ላይ የተመሰረተውን ግብርናቸውን በማሻሻል ዓመቱን ሙሉ ማምረት እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።


ሌላው አቶ ጫንያለው ያደታ ደግሞ የመስኖ ግድቡ በግብርና ስራ እያከናወኗቸው ባሉ የተለያዩ ኢኒሼቲቮች ላይ ያላቸው ተሳትፎ እንዲጨምር ይረዳል ብለዋል።


በአካባቢያቸው ሌሎች የግብርና ስራዎችም ላይ ጠንክረው በመስራት ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚያግዛቸው አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025