
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት ማሳደጉን በኢትዮጵያ የናይጄሪያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን ኃላፊ አምባሳዶር ማክስ ኦቤዴ ገለጹ።
ምክትል ሚሲዮን ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ የረጅም ጊዜ ስትራቴጂክ አጋርነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተዋል።
የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የናይጄሪያ ባለሃብቶችን ቀልብ መሳቡን ተናግረዋል።
ማሻሻያውን ተከትሎ በርካታ የናይጄሪያ ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በዘርፉ የመሰማራት ፍላጎት መጨመሩንም ገልጸዋል።
የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ቀደም ሲል የጀመረ መሆኑን ጠቁመው፤ የናይጄሪያ ባለሃብቶች በሲሚንቶ ምርት፣ በምግብና መጠጥ ዘርፎች መሰማራታቸውን አንስተዋል።
የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የባንክ ዘርፉን ጨምሮ በርካታ የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ነው የተናገሩት።
እንደ ምክትል አምባሳደሩ ገለጻ ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ በርካታ የህዝብ ቁጥርና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው ናቸው።
ሀገራቱ በቀጣይም በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ግንኙነታቸውን የበለጠ በማጠናከር በአፍሪካ የመሪነት ሚናቸውን ይወጣሉ ብለዋል።
ሀገራቱ የብዝሃ ባህል፣ ሃይማኖት እና ቋንቋ ባለቤት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድም በሳምንት ሶሰት ቀን ወደ ናይጄሪያ የሚያደርገው በረራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን የበለጠ ለማጠናከር ወሳኝ ሚና አለው ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ የጀመሩት እአአ በ1964 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025