
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ባለሀብቶች በጅማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሰማሩ ከመንግስት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ።
አምባሳደር ቼን ሃይ የጅማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎብኝተዋል።
አምባሳደሩ በጅማና አካባቢው በስፋት የሚመረተውን አቮካዶ በግብዓትነት በመጠቀም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያዎች የሚልከውን አክሻይ ጀይ ኩባንያ የምርት ሂደትና አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ በጅማና አካባቢው ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ማቀነባበር የሚያስችል መብራት፤ ውሃ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች መኖራቸውን ከጉብኝቱ መረዳት መቻላቸውን ተናግረዋል።
ቻይናውያን ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ከኮርፖሬሽኑ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አመልክተዋል።

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ዘርፍ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ በበኩላቸው የቻይና ባለሃብቶች ተሳትፎ ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ነጻ የንግድ ቀጣና ከጊዜ ወደ ጊዜ ይበልጥ እያደገ የመጣና ቀዳሚ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮርፖሬሽኑ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ጋር በኢንቨስትመንት እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት፤ በእውቀትና ክህሎት ሽግግር ጭምር ያለውን ትብብር ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ነው ብለዋል።
አያይዘውም ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞንነት በመሸጋገር ሂደት ላይ ያሉ ተጨማሪ የኢንቨስትመንትና በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የሪፎርም ተግባራትን አንስተዋል።
ቻይናውያን ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ ምቹ አማራጮችን ተጠቅመው በዘርፉ እንዲሰማሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025