የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቻይና ባለሀብቶች በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ በኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሰማሩ በቅንጅት ይሰራል - አምባሳደር ቼን ሃይ

Apr 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ባለሀብቶች በጅማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሰማሩ ከመንግስት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ።

አምባሳደር ቼን ሃይ የጅማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎብኝተዋል።

አምባሳደሩ በጅማና አካባቢው በስፋት የሚመረተውን አቮካዶ በግብዓትነት በመጠቀም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያዎች የሚልከውን አክሻይ ጀይ ኩባንያ የምርት ሂደትና አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ በጅማና አካባቢው ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ማቀነባበር የሚያስችል መብራት፤ ውሃ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች መኖራቸውን ከጉብኝቱ መረዳት መቻላቸውን ተናግረዋል።

ቻይናውያን ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ከኮርፖሬሽኑ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አመልክተዋል።


የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ዘርፍ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ በበኩላቸው የቻይና ባለሃብቶች ተሳትፎ ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ነጻ የንግድ ቀጣና ከጊዜ ወደ ጊዜ ይበልጥ እያደገ የመጣና ቀዳሚ መሆኑን ገልጸዋል።

ኮርፖሬሽኑ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ጋር በኢንቨስትመንት እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት፤ በእውቀትና ክህሎት ሽግግር ጭምር ያለውን ትብብር ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ነው ብለዋል።

አያይዘውም ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞንነት በመሸጋገር ሂደት ላይ ያሉ ተጨማሪ የኢንቨስትመንትና በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የሪፎርም ተግባራትን አንስተዋል።

ቻይናውያን ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ ምቹ አማራጮችን ተጠቅመው በዘርፉ እንዲሰማሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025