የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ ከተመድ ጋር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን ትብብር የማሳደግ ፍላጎት አላት- ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከተባበበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሻ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።


በውይይቱ ላይ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ሽግግር እንዲሁም በሌሎች መስኮች ላይ ያላትን ዓለም አቀፍ ትብብርን የማሳደግ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።

በዚህ ረገድም ኢኖንፎርሜሽ እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በዲጂታል ቴክኖሎጂ በፈጠራቸው ማዕቀፎች ያላትን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንደምትሰራ አመልክተዋል።

ከተመድ የቴክኖሎጂ የስራ ክፍሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ይሰራል ነው ያሉት።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በመሰረተ ልማት፣ በአስተዳደርና በሰው አቅም ግንባታ ላይ በማተኮር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገት የሚያጎለብቱ ጠንካራ ፖሊሲዎች እና ተቋማት ማቋቋሟን በውይይቱ ወቅት አንስተዋል።


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) የደቡባዊ ንፍቀ ክበብ ሃገራት በዲጂታል ዓለም እኩል ተጠቃሚ እና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የአሰራር ማዕቀፎች ላይ ማሻሻያ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የተመድን የዲጂታል ዘርፍ እድሎችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ማቅረባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025