አሶሳ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ):- በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተመራጮች ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ተወያዩ።
ውይይቱ የተደረገው የህዝብ ተወካዮቹ በክልሉ ከመራጮች ጋር ምክክር ሲያደርጉ ቆይተው የተነሱ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ ነው።
በውይይቱ ላይ ሪፖርት ያቀረቡት የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል አቶ ሙባረክ ኤሊያስ፤ ከህብረተሰቡ ጋር በተደረገው ውይይት የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መነሳታቸውን ጠቅሰዋል።
ለአብነትም የፌዴራል መንግስትን እገዛ የሚጠይቁ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እጥረት፣ የኔትወርክ ማሻሻያ፣ የመንገድ እና ሌሎች የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ተነስተዋል ብለዋል።
የክልሉ መንግስት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል፣ የጤና ተቋማት ግንባታ እና የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ተጠይቋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሐሰን በበኩላቸው፤ በህብረተሰቡ የተነሱት የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በተለይ የመንገድ እና የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማስፋፋት ከፌዴራል መንግስት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የውይይት መድረክ እየተካሄደ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ -ጉባዔ አስካለች አልቦሮን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራር አባላት ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025